፠፠፠ የተኮሳተረ አገሩን የሚያልም፥ ተስፋ የገመደ ግንባር ይታየኛል፡፡ እንደራሱ ጸጉር ነፍጥና ጀግነነት፥ ወኔና ወንድነት አጣምሮ ገምዷል፡፡ ሎሚታ ያስጌጠው የእሳት ጎራዴ ፥ ካፎቱ ተመዝዞ ከሰገባው ወጥቷል፡፡ እሳት የሚተፋ ሽጉጡን በሽንጡ፥ በወገብ ሸጉጧል፡፡ ስልጣን የተራበ፥ ይሁዳ አሰፍስፎ በባንዳነት ወጉ፥ ክብሩን አሳልፎ በባዕዳን ጉቦ ፥ወንድሙን የሚሸጥ ፥ መቅደላን ከቧታል ቀኙን የሚተካው ፊታውራሪ፥ ገብሬ ህያው አሸልቦ ባንዳ ባሰለፈው በእንግሊዝ፥ ሰራዊት ቴዎድሮስ ተከቦ በራሱ ሊወስን ፥ወንድ አንድ ሰው ቆሟል (ውሳኔ ቴዎድሮስ) ‹‹ለጠላት ክንዴን ሰጥቼ፥ ኢትዮጵያን ከማዋርዳት ! የከበረችው ሀገሬን ፥በቁም መሞቷን ከማዬት ! እኔ ልቅደማትና ፥ትውልድ ወንድነት ይማር ! እንዲሰጥ ይረዳሉና ፥የንጉስ ነፍሱ ለሀገር ፡፡ እሳቱ ክንዴን ጨብጠው ፥ ዘላለም ከሚፎክሩ! አሩሩን ልጉረሰውና ይከበር ያበሻ ክብሩ ፡፡ ›› አለና ካሳ ወሰነ ምንም ፍርሃት ሳይገደው እሳቱን ባፉ ጎረሰ ፥ወንዱ ወንድነት ሲገባው (ቀጥሎ!) አንድ ኢትዮጵያ የሚል ፥አንድ ጀግና ወድቋል የለበሰው ልብሱ ፥በደም ተጨማልቋል ሱሪ የታጠቀ ወንድ አንድ ሰው ሞቷል፡፡ ነፍጠኝነት ዘሩን፥ ሀበሻዊ ክብሩን ኢትዮጵያዊ ደሙን ፥ በደሙ ገምዶ መቅደላ መኻል ላይ ለራሱ ሳይሰስት ካሳችን ተማግዶ ከአፈሙዝ በወጣ በገዛ ሽጉጡ ወደቀ ቴዎድሮስ በጁ እሳት ነዶ፡፡ (ቀጠለ!) ባንዳ ያሰለፈ ፈረንጅ አሰፍስፎ ሊማርክ ሲጠጋ ቴወድሮስን ጠልፎ መቅደላ ሲገቡ ንጉሱ ካለበት የወንዶች ወንድ ወድቆ ጩኸት በበዛበት እሳት የጎረሰ እሳት አስተዋሉ ያበሻን ጀግንነት ከካሳ ተማሩ፡፡ አሁንም ተነሱ ! ግብረ ቴዎድሮሶች የድሮ ስርአት ዳግም ናፋቂዎች የተቆጣ ስሜት ከፈላ ደም ጋር ባንድነት ቀይጠው ሀውልቱን ገነቡ በደም ባጥንታቸው ካዚያማ! አፍራሽ ገባውና መሰረቱን ሊጥል ሌት ተቀን ሲለፋ ተቆጣ ደማቸው ቤታቸው ሲገፋ ክብራቸው ሲጠፋ የነፍጠኛ ልጆች ነፍጥ ይዘው ተነሱ ያባታቸውን ክብር ዳግም ሊመልሱ (ዘላለም በላይነህ)
Tuesday, 16 January 2018
ዝክረ ቴዎድሮስ
፠፠፠ የተኮሳተረ አገሩን የሚያልም፥ ተስፋ የገመደ ግንባር ይታየኛል፡፡ እንደራሱ ጸጉር ነፍጥና ጀግነነት፥ ወኔና ወንድነት አጣምሮ ገምዷል፡፡ ሎሚታ ያስጌጠው የእሳት ጎራዴ ፥ ካፎቱ ተመዝዞ ከሰገባው ወጥቷል፡፡ እሳት የሚተፋ ሽጉጡን በሽንጡ፥ በወገብ ሸጉጧል፡፡ ስልጣን የተራበ፥ ይሁዳ አሰፍስፎ በባንዳነት ወጉ፥ ክብሩን አሳልፎ በባዕዳን ጉቦ ፥ወንድሙን የሚሸጥ ፥ መቅደላን ከቧታል ቀኙን የሚተካው ፊታውራሪ፥ ገብሬ ህያው አሸልቦ ባንዳ ባሰለፈው በእንግሊዝ፥ ሰራዊት ቴዎድሮስ ተከቦ በራሱ ሊወስን ፥ወንድ አንድ ሰው ቆሟል (ውሳኔ ቴዎድሮስ) ‹‹ለጠላት ክንዴን ሰጥቼ፥ ኢትዮጵያን ከማዋርዳት ! የከበረችው ሀገሬን ፥በቁም መሞቷን ከማዬት ! እኔ ልቅደማትና ፥ትውልድ ወንድነት ይማር ! እንዲሰጥ ይረዳሉና ፥የንጉስ ነፍሱ ለሀገር ፡፡ እሳቱ ክንዴን ጨብጠው ፥ ዘላለም ከሚፎክሩ! አሩሩን ልጉረሰውና ይከበር ያበሻ ክብሩ ፡፡ ›› አለና ካሳ ወሰነ ምንም ፍርሃት ሳይገደው እሳቱን ባፉ ጎረሰ ፥ወንዱ ወንድነት ሲገባው (ቀጥሎ!) አንድ ኢትዮጵያ የሚል ፥አንድ ጀግና ወድቋል የለበሰው ልብሱ ፥በደም ተጨማልቋል ሱሪ የታጠቀ ወንድ አንድ ሰው ሞቷል፡፡ ነፍጠኝነት ዘሩን፥ ሀበሻዊ ክብሩን ኢትዮጵያዊ ደሙን ፥ በደሙ ገምዶ መቅደላ መኻል ላይ ለራሱ ሳይሰስት ካሳችን ተማግዶ ከአፈሙዝ በወጣ በገዛ ሽጉጡ ወደቀ ቴዎድሮስ በጁ እሳት ነዶ፡፡ (ቀጠለ!) ባንዳ ያሰለፈ ፈረንጅ አሰፍስፎ ሊማርክ ሲጠጋ ቴወድሮስን ጠልፎ መቅደላ ሲገቡ ንጉሱ ካለበት የወንዶች ወንድ ወድቆ ጩኸት በበዛበት እሳት የጎረሰ እሳት አስተዋሉ ያበሻን ጀግንነት ከካሳ ተማሩ፡፡ አሁንም ተነሱ ! ግብረ ቴዎድሮሶች የድሮ ስርአት ዳግም ናፋቂዎች የተቆጣ ስሜት ከፈላ ደም ጋር ባንድነት ቀይጠው ሀውልቱን ገነቡ በደም ባጥንታቸው ካዚያማ! አፍራሽ ገባውና መሰረቱን ሊጥል ሌት ተቀን ሲለፋ ተቆጣ ደማቸው ቤታቸው ሲገፋ ክብራቸው ሲጠፋ የነፍጠኛ ልጆች ነፍጥ ይዘው ተነሱ ያባታቸውን ክብር ዳግም ሊመልሱ (ዘላለም በላይነህ)
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
ጠወለገች አሉ!!
ጠወለገች አሉ!! አባይ ወዲያ ማዶ ከተከዜ ግርጌ የበቀለች ወይን የቆመች ብሳና ጠወለገች አሉ ሰው አጣለችና!!! የግዮን አገር ሰው ታሪክን የሰራ በተወለደበት እንዴት ...
-
፠፠፠ የተኮሳተረ አገሩን የሚያልም፥ ተስፋ የገመደ ግንባር ይታየኛል፡፡ እንደራሱ ጸጉር ነፍጥና ጀግነነት፥ ወኔና ወንድነት አጣምሮ ገምዷል፡፡ ሎሚታ ያስጌጠው የእሳት ጎራዴ ፥ ካፎቱ ተመዝዞ ከሰገባው ...
-
ህግ እንደተርጔሚው …..ተብሎ ከተጣፈ ገመና ሼፋኜን ቤቴን ልስራ ባለ……ህግ ከተላለፈ መዝግቡኝ ናሳዎች ….ወደማርስ ልሄድ ነው ከምድር አልችልም ….መሬት ለመንግስት ነው!!! ‹‹‹‹‹‹‹‹‹እዩት ይሄ...
-
ጠወለገች አሉ!! አባይ ወዲያ ማዶ ከተከዜ ግርጌ የበቀለች ወይን የቆመች ብሳና ጠወለገች አሉ ሰው አጣለችና!!! የግዮን አገር ሰው ታሪክን የሰራ በተወለደበት እንዴት ...

No comments:
Post a Comment