----------//----------------
እንኳን አደረሰህ--- አትበይኝ ፍቅሬ----እርግማን ነው ለኔ
ጠፈፍ እንኳ ሳይል --- የደማው ውስጠቴ---- የቆሰለው ቁስሌ፡፡
-------//-----------
አዲስ በሚል ሰበብ ----ሞት ሲደገስልኝ
እንኳን ደረስህ ---አትበይኝ ፍቅሬ--- ይልቅ አልቅሽልኝ፡፡
---------*****----------
(ስሚኝማ ውዴ)
እንኳን አደረሰህ--- አትበይኝ ፍቅሬ----እርግማን ነው ለኔ
ጠፈፍ እንኳ ሳይል --- የደማው ውስጠቴ---- የቆሰለው ቁስሌ፡፡
-------//-----------
አዲስ በሚል ሰበብ ----ሞት ሲደገስልኝ
እንኳን ደረስህ ---አትበይኝ ፍቅሬ--- ይልቅ አልቅሽልኝ፡፡
---------*****----------
(ስሚኝማ ውዴ)
ለዘመኑ ብስራት ---- በባዕል ዋ! ዜማ
ባልነበረ ታሪክ --- ግፋቸው ሲሰማ
መድፍ ይተኩሳሉ----በመለከት ፋንታ
ለድንበር የሚሞት-- ወታደር ይመስል-- የጦር መሪ ጋንታ
(---ከ
------ዚ
---------ያ ----ይቀጥላል)
በማታለል ዘዬ----- በቸከ ቅላፄ
ዘወትር ሲያላዝን -----ደም የዋጠው አፄ
ለጀብጀቦ አጎብዳጅ------ ለቸከ ህሌና
መድፍ እየተኮሱ------ ሊያደርቁን ነውና፡፡
---//-----
(አይገርም የኔ ውድ!!)
ግዳይ እንደጣለ--- እንደ አባይ ልጅ አዳኝ
እንደ አባ ታጠቁ--- እንደ አንበሳ ገዳይ
ሊላዝንብን ነው-- ባላየነው እውነት-- በማይገባን ዜማ
በማታለል ቅኔ --በለበጣ ቃላት----- ልባችን ሊደማ፡፡
(ተመልከች የኔ ውድ)
የደርሶ መልስ --አመት መከራ--- ሊያበስረን
የበግ ደም ሰውቶ-- በየአደባባዩ---- እንቁ ጣጣሽ ሊለን
ካራውን ይስላል------በጎቹን ሰውቶ--- ለበጎች ሊየበላን፡፡
(ይ*ታ*ይ*ሽ* እንግዲ----)
የበግ ስጋ ለበግ-- በየትኛው ሀገር -- ተ-በ-ል-ቶ ያውቃል
ማንስ ይሄን አ’ርጎ---ለህዝበ አዳም ልጆች--- አስደስቶ ውሏል
ባላየነው እውነት ባልሰማነው ዜማ ሀሴት ይስተጋባል???
*********//*********
(ስለዚህ ፍቅሬ ሆይ)
እንኳን አደረሰህ ---አትበይኝ ፍቅሬ-----እርግማን ነው ለኔ
ጠፈፍ እንኳ ሳይል -- የደማው ውስጠቴ--- የቆሰለው ቁስሌ
አዲስ በሚል ሰበብ ----ሞት ሲደገስልኝ
እንኳን አደረስህ ---አትበይኝ ፍቅሬ--- ይልቅ አልቅሽልኝ፡፡
(ምክንያቱም---- ውዴ)
ዋ! ዜማን ደግሰው ----ለአዲስ አመት ብስራት
እየተሳለቁ ------በሞተ ማንነት
አድምጡ ይሉናል--- ቅኝት አልባ ዘፈን
ቁና ሙሉ ስቃይ--- መከራን ሲያበስሩን
ደስታነው ብለው-- ዋ!ዜማን ሲነግሩን
******///********
እና ‘ሄን እያየሽ--- የምን መልካም ዘመን--- የምን አዲስ አመት
ለገደሉት ውስጤ ------ሞት ሲደገስለት?
(ምን አልባት የኔ ውድ)
ኤልያስ ከመጣ----- ደመና ተላብሶ
የነሱን ዋ!! ዜማ---- ድግስ አስቀይሶ
አዲስ ዘመን ካየን--- ከሞታችን ጀርባ
ያን ጊዜ ትያለሽ------- በተቀኜ ዜማ
ምን አልባት የኔ ውድ
ዝናቡ ካባራ ------ደምን የሚያዘንበው
መድፉን በመለከት----- ቀይሮ ካየነው
አዲስ አመት መባል------ ለኔ ያን--- ጊዜ ነው፡፡
(ስለዚህ ፍቅሬ ሆይ)
እንኳን አደረሰህ ---እንዳትይኝ ዛሬ -እርግማን ነው ለኔ
ጠፈፍ እንኳ ሳይል -- የደማው ውስጠቴ--- የቆሰለው ቁስሌ
አዲስ በሚል ሰበብ ----ሞት ሲደገስልኝ
እንኳን አደረስህ ---አትበይኝ ፍቅሬ--- ይልቅ አልቅሽልኝ፡፡
(ዜዶ ነኝ የብእር አይኖች ከፈቱ)

No comments:
Post a Comment